የጸጋውን ቁርበት
ግጥምና ዜማ - ኢየሩሳሌም ነጊያ
ሙዚቃ ቅንብር - ሮቤል እንዳለ
ጊታር -አቤኔዘር ዳዊት
ሚክስ ና ማስተሪንግ ንፁህ ይልማ
ሞሽን ግራፊክስ - ቲራጎ ታደሰ
/ @eyitagraphicsmotion
#Addis_Ababa #Eyerusalem_Negiya #Volume_3
የፍጥረት በኩር መጀመሪያ
ፍፃሜ የሆነ መደምደምያ
የሚታይ የማይታየው ዓለማቱ
በእርሱ ተፈትሮዋል ነው ምክንያቱ
የአዳምን እርቃን ሸፈነ ያን ሀፍረት
ህይወት አለበሰው የፀጋውን ቁርበት
የእባቡን እራስ ቀጥቅጦ የቀጣ
በሴቲቱ ዘር ግንድ በስጋ የመጣ
ከጥፋቱ ውሀ መርከብ የሚጠብቅ
የማምለጫው መንገድ እንዲድን ፃድቅ
በይስሀቅ ምትክ የታረደው በግ
በበሩ መቃን ላይ የተረጨው ደም
ነፍሴ በፍቅሩ ገመድ ታስረች፪
አየሱስ እየሱስ አለች
ነውር የሌለበት ንፁህ መስዋት
ጣፋጩ ሽታ በእግዚአብሔር ፊት
የመስዋቱ በግ ሊቀ ካህኑ
ስለኛ የሚታይ በመቅደሱ
ከሰማይ ሰማያት የወረደው መና
የፀናው አለት ያፈለቀው ውሀ
የመውጫው መስላል ከምድር ወደ ስማይ
የማህዘን እራስ ክቡር ህያው ድንጋይ
የሁሉ ፊተኛ ጅማሬ ፍፃሜ
የህይወት ምህራፍ ከፋች ደግሞም ድምዳሜ
የፍጥረት እስትንፋስ ህልውና መሪ
ፊተኛ ቀዳሚ የአለም ፈጣሪ
ኢየሱስ ጥንትም የነበር
ኢየሱስ ዛሬም ደግሞ ያለ
ኢየሱስ ዘላለም የሚኖር
ኢየሱስ ሁሌ እንደክበረ
ከላይ ከአርያም ከክብር ዙፋኑ
ከተንቆጠቆጠው ካማረው መንበሩ
ወርዶ በኛ መሀል ድንኳኑን ተከለ
ቃል ስጋ በመሆን በእኛ አደረ
ከሀጢያት በስተቀር በሁሉ ያለፈ
ሲኦልን ድል ነስቶ ሞትን ያሸነፈ
መንግስቱ በምድር ሁሉ ሊጠቀልል
ሊነግስ ዘላለም ተመልሶ ይመጣል
ያለ የነበረ አልፋና ኦሜጋ
አንዳች ፍትረት የለም ክብሩን የሚጥጋ
ከስሞች የሚበልጥ ስምም ተስትቶታል
ያልልክ እግዚአብሔር ከፍ ከፍ አድርጎታል
ኢየሱስ ጥንትም የነበር
ኢየሱስ ዛሬም ደግሞ ያለ
ኢየሱስ ዘላለም የሚኖር
ኢየሱስ ሁሌ እንደክበረ
ነፍሴ በፍቅሩ ገመድ ታስረች
በዐይኑዋ ማዳኑን አየች
ነፍሴ በፍቅሩ ገመድ ታስረች
አየሱስ እየሱስ አለች
መስቀልህ በልቤ እንዲሳል ደምቆ
ማንነህ እንዲታይ በእኔ ልቆ
ይህ ጥማት በውስጤ ስርፆ ገባ
እፋልግሀለውነጋ ጠባ